Discover
DW | Amharic - News

4696 Episodes
Reverse
ይህ “የጤና አልጎሪዝም” የተሰኘው አዲስ እና ባለ 10 ክፍል የዶቸ ቬለ በማድመጥ መማር ድራማ ነው። በዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንዛቤ ላይ የሚያተኩረው ድራማ ደራሲ ጄምስ ሙሐንዶ ይባላል። በፍጥነት እያደገ ወደ ሚገኘው የአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ዓለም በመዝለቅ በዕለት ተለት ሕይወታችን ላይ ምን አይነት ተጽዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ይመለከታል።
የአውሮፓ ህብረት የመርማሪዎች ቡድን (ECA) በአውሮፓ ኮሚሽን የአፍርካ የምግብ እርዳታ ክንውን ላይ ባወጣው የምርመራ ዘገባ፤ ህብረቱ ባለፉት አመታት በአፍርካ ለረሀብ ለተጋለጡና የምግብ እጥረት ላለባቸው አካባቢዎች የሰጠው እርዳታ፤ የጠና እረሀብ ላላባቸውና አስቸኳይ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ህዝቦች በትክክል እንደማይደርስ አጋልጧል።
በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ እና ዉጫሌ ከተሞች አቅራቢያ የተጠለሉ ተፈናቃዮች ለከፍተኛ የምግብ እጥረት ተጋልጠናል አሉ ። ተፈናቃዮቹ እንዳሉት እስከ ሰባት ወራት ልዩነት ይቀርብ የነበረው አነስተኛ መጠን ያለው ምግብ አሁን እስከ መቋረጥ ደርሷል ።
የናጄሪያ፣ የደቡብ አፍሪቃ፣ የሴኔጋል፣ የጊኒ ቢሳዉ፣ የቶጎና የሌሎቹም የአፍሪቃ ሐገራት የተፈጥሮ ጥበቃ ተሟጋቾች፣ ባለሙያዎችና ምሑራን ባንድ ነገር አንድ ናቸዉ።ከዚሕ ቀደም ከተደረጉ ጉባኤዎች ሁሉ በዘንድሮዉ ጉባኤ የአፍሪቃን ችግር ለተቀረዉ ዓለም ለማሳወቅ የተሻለ እድል አግኝተዉበታል-በሕዝብ ጉባኤ።
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ዓለም አቀፍ ችግሮችን ለመፍታት በጋራ መተባበር እንደሚያስፈልግ አሳስሰቡ። ራማፎሳ ይህንን ያሉት ዛሬ በደቡብ አፍሪካ አስተናጋጅነት መካሄድ የጀመረውን የቡድን 20 ጉባኤ መክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ ነው።
በሰሜን ኢትዮጵያ ፤ትግራይ ክልል ተጨማሪ ጥቃቶችን ለመከላከል ጉዳዩ ያሳሰባቸው መንግስታት እርምጃ መውሰድ አለባቸው ሲል ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ሂውማን ራይትስ ወች አሳሰበ
እንደ ኢትዮጵያ፣ ማሊና ዩጋንዳን የመሳሰሉ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸዉ ሐገራት መንግሥታት ለጤና ጥበቃ የሚመድቡት ገንዘብ እጅግ በጣም ትንሽ መሆኑን የዓለም ባንክ አስታዉቋል። ድሆቹ ሐገራት መንግስታት ለጤና የሚመድቡት ገንዘብ የዓለም ባንክ መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ለማዳረስ ያስፈልጋል ከሚለዉ ዝቅተኛ ተመን እንኳ በእጅጉ ያነሰ ሲል የዓለም ባንክ ገለፀ።
የውጭ ምንዛሪ ግብይት በአቅርቦት እና ፍላጎት እንዲወሰን ከተደረገ ወዲህ ኢትዮጵያ ከሸቀጦች የወጪ ንግድ የምታገኘው ገቢ ዕድገት ቢያሳይም ብር እየተዳከመ ነው። የወርቅ ኤክስፖርት መሻሻል ብር እንዲረጋጋ ሊያደርግ እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ ተስፋ አድርጓል። ሦስት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይት የምንዛሪ ገበያው ብር ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ይፈትሻል።
ትራምፕ በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው በG20 ጉባኤ ላይ የአሜሪካ ባለስልጣናት እንደማይገኙ ገለፁ።ትራምፕ ባለስልጣኖቻቸው በስብሰባው የማይገኙት ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ስርዓታዊ በሆነ መንገድ ነጭ የሀገሪቱ ዜጎች “ተገደለዋል እና ተጨፍጭፈዋል” በሚል ነው።
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ሊጠናቀቅ የቀረዉ ሦስት ወራት ገደማ ነዉ። ኮሚሽኑ ከህዝብ ያሰባሰባቸዉን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ለመንግሥት ያቀርባል።በሌላ በኩል በያዝነዉ 2018 ዓመት ብሔራዊ ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል። ይሁንና መንግሥት ከህዝብ ለተሰበሰቡት አጀንዳዎች ከምርጫ መፊት መልስ ለመስጠት ጊዜና አቅም ይኖረዉ ይሆን?
ህወሐት በአለፈው እሁድ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስትን የፕሪቶርያ ውል በመጣስ በትግራይ ግጭት ለመፍጠር በአፋር እና በምዕራብ ትግራይ ታጣቂዎች እየመለመለ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
ብሪታንያ፣ ካናዳ እና አውስትራሊያ በዛሬው ዕለት ለፍልስጤም መንግስትነት በይፋ እውቅና ሰጡ። ርምጃውን የፍልስጤም መብት ደጋፊዎች መደበኛ እውቅና ለማግኘት የመጀመሪያው ጥረት ነው ሲሉ፤ በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ ዘንድ ውግዘት አስከትሏል።
በወንዶች የ29 አመቱ ስባስቲያን ሳዌ ያሸነፈ ሲሆን፤ ይህ ውጤት በለንደን ማራቶን ካሸነፈ ከአምስት ወራት በኋላ የተመዘገበ መሆኑ ነው።በሴቶችም ሌኛዋ የሀገሩ ልጅ ሮዝሜሪ ዋንጂሩ ፉክክሩን በአንደኛነት ጨርሳለች።ባለፈው አመት በተካሄደው የበርሊን ማራቶን በወንዶች ሚልኬሳ መንገሻ፤ በሴቶች ትግስት ከተማ ለኢትዮጵያ ድርብ ድል አስገኝተው ነበር።
ኢትዮጵያ ስትካፈልበት ከሰነበተችው 20ኛው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ሳታገኝ የመጨረሻውን ቀን እየጠበቀች ነው። ዛሬ ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ5000 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት አራት ጄኔራልነትን ጨምሮ ለ66 ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንኖች ማዕረጎች ሰጠ። ሉቴናንት ጄኔራል አለምሸት ደግፌ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ደስታ አብቼ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ይመር መኮንን እና ሉቴናንት ጀኔራል ድሪባ መኮንን ሙሉ ጄኔራል ሆነዋል።
የማሊ፣ ኒጀር እና የቡርኪናፋሶ መንግሥታ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተገረሱ በኋላ ከሁለት ዓመታት በፊት የተመሰረተዉ የሳህል ግዛቶች ህብረት (AES) በያዘዉ ያልተሟሉ ግቦች እና የኢኮኖሚ ተስፋዎች ብሎም ሚዛናዊ ያልሆኑ ጥቅሞች በማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪናፋሶ ትችቶች ገጥሞታል። ህብረቱ ዛሬ እስከ ምን ድርሶ ይሆን?
ደቡብ ሱዳን አዲስ የእርስ በርስ ግጭት አፋፍ ላይ ያለች ይመስላል። ከጎርጎረሳዉያኑ 2018 ጀምሮ በሃገሪቱ የነበረዉን ከፍተኛ የእርስ በእርስ ጦርነት ያስቆመዉ የሰላም ስምምነት በተለይ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር በአገር ክህደት እና በሌሎች ወንጀሎች ከተከሰሱ እና እስር ላይ ከዋሉ በኋላ የሰላም ስምምነቱ ዳመና ያጠላበት ይመስላል።
ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ዎባ ኣሪ ወረዳ ለጊዜው “ ምንነቱ ያልታወቀ “ ባሉት ተባይ የአርሻ ማሳቸው መወረሩን አርሶ አደሮች ተናገሩ ፡፡ ተባዩ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው የሰብሎችን ፈሳሽ በመምጠጥና በማድረቅ መሆኑን የተናገሩት አርሶአደሮቹ ተባዩ ከሳምንት በፊት በአካባቢው ከታየ በኋላ ቀስ በቀስ ወደ መንጋነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል ፡፡
ለሦስት ዓመት ተኩል በትብብር ሲሠሩ የቆዩ አምስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ዛሬ መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ቅንጅት መሠረቱ። "ኢትዮጵያ የህልውና አደጋ ውስጥ ናት" የሚለው ድምዳሜ የቅንጅቱ መመሥረት ዐቢይ መነሻ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን ቀጠና “ሰላም ለማጠናከር ባላት ቁርጠኝነት” እንደተበረታቱ በአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ተናገሩ። ቡሎስ ይኸን ያሉት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር በኩል ወደብ ሊኖራት ይገባል በሚል የሚያራምደው አቋም ውጥረት በፈጠረበት ወቅት ነው።























