DiscoverDW | Amharic - News
DW | Amharic - News
Claim Ownership

DW | Amharic - News

Author:

Subscribed: 53Played: 3,489
Share

Description

News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
4711 Episodes
Reverse
ሰውሰራሽ አስተውሎት በዓለም ላይ በፍጥነት እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ነው።ቴክኖሎጂው ትምህርትን ግላዊነት በማላበስ፣ በቂ አገልግሎት ለሌላቸው ተማሪዎች ተደራሽነትን በማሻሻል በአፍሪካ በትምህርት ላይ በጎ ተጽእኖ እያሳደረ ነው።ያም ሆኖ ቴክኖሎጂውፈተናዎችም አሉት።ባለሙያዎች ፈተናዎቹን ለመሻገር ቴክኖሎጂው የሚገዛበት ፖሊሲዎች ማውጣትን ይመክራሉ።
የ5 ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» የተሰኘው ቅንጅት ከመጭው ምርጫ በፊት የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ሰላም እንዲያሰፍን ጠየቀ። ትብብሩ ያለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ የታሰሩ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች እንዲፈቱም ጠይቋል። መንግስት ለዚህ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥም ትብብሩ ቀነ ገደብ አስቀምጧል።
ልዑል አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሠልማን ዩናይትድ ስቴትስን ሲጎበኙ ከ7 ዓመት ወዲሕ የመጀመሪያቸዉ ነዉ።ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በመካከለኛዉ ምሥራቅ «ምትክ የሌላቸዉ» መሪ ላሏቸዉ ልዑል ያደረጉት አቀባበልም ልዩ ነዉ።ልዑሉ ራት ተጋበዙ፣ ዋይት ሐዉስ፣ ቀይ ምንጣፍ ተዘረጋ፣ የክብር ዘቡ ተሰለፈ፣ ማርሹ ተንቆረቆረ----
አነጋጋሪው የጄፌሪ ኤፕስታይን የወሲብ ቅሌት ሰነድ ይፋ እንዲደረግ የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች እና ሴኔት በአብላጫ ድምፅ ወሰኑ ። የሕግ አውጭዎቹ ባለሥልጣናትን ጨምሮ የታዋቂ ሰዎችን የወሲብ ቅሌት ይዟል የተባለው ሰነድ ይፋ እንዲሆን ድጋፍ ከማግኘቱ በፊት ለዓመታት የዘለቀ ተቋማዊ ክህደት ተፈጽሞበት እንደነበር የጥቃቱ ሰላባዎች ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የመማሪያ መጻሕፍት አታሚ ድርጅት እና የወጣቶች የኢንቨስትመንት ባንክ ጨምሮ በዚህ ዓመት አምስት ኩባንያዎች እንደሚያቋቁም አሳውቋል። ከሁለት የሩሲያ ኩባንያዎች ጋር የመግባቢያ ሥምምነቶች የተፈራረመው ተቋም ከ2011 ጀምሮ የስኳር ፋብሪካዎች ለመሸጥ ሲደረግ የነበረው ጥረት አቋርጧል።
ናማታኒ ክዌክዌዛ በ18 ዓመቷ ነበር WELEAD TRUST የተባለ ወጣት መሪዎችን የሚያሰለጥንና በፖለቲካ ውሳኔዎች ሂደቶች እንዲሳተፉ የሚሠራ ድርጅት የመሠረተችው።በተባባሰው የዚምባብዌ ጨቋኝ ድባብ ክዌክዌዛ ለሕግ የበላይነትn ለፖለቲካዊ ተሳትፎ ትታገላለች፤ታስራለች፤ቁም ስቅልና የማስፈራሪት ሙከራዎች ደርሰውባታል። ስኬት ዋጋ ያስከፍላል ትላለች።
የዝግጅቱ አስተባባሪ የሆኑት የታሪክ መምህርና የማኀበራዊ ጉዳይ ባለሙያ አቶ ተፈራ ኃይሉ፣የሰሞኑበክብረ በዓል፣እንደ ሻምበል ከተማ ጆባ ሁሉ በኮሪያ ዘመቻ ለተሳተፉ ኢትዮጵያውያን አርበኞች ምስጋና ለማቅረብ የተዘጋጀ እንደነበር ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
«ተግባራዊ ባይሆኑ ተወያይተን የምወስዳቸው ጠንካራ እርምጃዎች ይኖራሉ። ዝርዝር ሄኔታውን በቅርቡ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።»
የውጭ ምንዛሪ ግብይት በአቅርቦት እና ፍላጎት እንዲወሰን ከተደረገ ወዲህ ኢትዮጵያ ከሸቀጦች የወጪ ንግድ የምታገኘው ገቢ ዕድገት ቢያሳይም ብር እየተዳከመ ነው። የወርቅ ኤክስፖርት መሻሻል ብር እንዲረጋጋ ሊያደርግ እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ ተስፋ አድርጓል። ሦስት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይት የምንዛሪ ገበያው ብር ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ይፈትሻል።
ምክርቤቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድና ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት በጻፈው ደብዳቤ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት የሕግ ማሻሻያ እንዲደረግ ጠይቋል።
የእናት ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ጌትነት ወርቁ፤ ነገር ግን መንግሥት በሐገሪቱ ሰላም ካስከበረ፤ ጦርነቶች ቆመው፣ የታሰሩት ተፈትተው፣ ያኮረፉት ኃይሎች ጋር የውይይትና የድርድር ሁኔታዎች ከተካሄዱ ምርጫው ሊካሄድ እንደሚችል ተስፋቸውን ይገልጻሉ።
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ሊጠናቀቅ የቀረዉ ሦስት ወራት ገደማ ነዉ። ኮሚሽኑ ከህዝብ ያሰባሰባቸዉን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ለመንግሥት ያቀርባል።በሌላ በኩል በያዝነዉ 2018 ዓመት ብሔራዊ ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል። ይሁንና መንግሥት ከህዝብ ለተሰበሰቡት አጀንዳዎች ከምርጫ መፊት መልስ ለመስጠት ጊዜና አቅም ይኖረዉ ይሆን?
ህወሐት በአለፈው እሁድ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስትን የፕሪቶርያ ውል በመጣስ በትግራይ ግጭት ለመፍጠር በአፋር እና በምዕራብ ትግራይ ታጣቂዎች እየመለመለ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
ብሪታንያ፣ ካናዳ እና አውስትራሊያ በዛሬው ዕለት ለፍልስጤም መንግስትነት በይፋ እውቅና ሰጡ። ርምጃውን የፍልስጤም መብት ደጋፊዎች መደበኛ እውቅና ለማግኘት የመጀመሪያው ጥረት ነው ሲሉ፤ በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ ዘንድ ውግዘት አስከትሏል።
በወንዶች የ29 አመቱ ስባስቲያን ሳዌ ያሸነፈ ሲሆን፤ ይህ ውጤት በለንደን ማራቶን ካሸነፈ ከአምስት ወራት በኋላ የተመዘገበ መሆኑ ነው።በሴቶችም ሌኛዋ የሀገሩ ልጅ ሮዝሜሪ ዋንጂሩ ፉክክሩን በአንደኛነት ጨርሳለች።ባለፈው አመት በተካሄደው የበርሊን ማራቶን በወንዶች ሚልኬሳ ​​መንገሻ፤ በሴቶች ትግስት ከተማ ለኢትዮጵያ ድርብ ድል አስገኝተው ነበር።
ኢትዮጵያ ስትካፈልበት ከሰነበተችው 20ኛው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ሳታገኝ የመጨረሻውን ቀን እየጠበቀች ነው። ዛሬ ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ5000 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት አራት ጄኔራልነትን ጨምሮ ለ66 ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንኖች ማዕረጎች ሰጠ። ሉቴናንት ጄኔራል አለምሸት ደግፌ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ደስታ አብቼ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ይመር መኮንን እና ሉቴናንት ጀኔራል ድሪባ መኮንን ሙሉ ጄኔራል ሆነዋል።
የማሊ፣ ኒጀር እና የቡርኪናፋሶ መንግሥታ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተገረሱ በኋላ ከሁለት ዓመታት በፊት የተመሰረተዉ የሳህል ግዛቶች ህብረት (AES) በያዘዉ ያልተሟሉ ግቦች እና የኢኮኖሚ ተስፋዎች ብሎም ሚዛናዊ ያልሆኑ ጥቅሞች በማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪናፋሶ ትችቶች ገጥሞታል። ህብረቱ ዛሬ እስከ ምን ድርሶ ይሆን?
ደቡብ ሱዳን አዲስ የእርስ በርስ ግጭት አፋፍ ላይ ያለች ይመስላል። ከጎርጎረሳዉያኑ 2018 ጀምሮ በሃገሪቱ የነበረዉን ከፍተኛ የእርስ በእርስ ጦርነት ያስቆመዉ የሰላም ስምምነት በተለይ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር በአገር ክህደት እና በሌሎች ወንጀሎች ከተከሰሱ እና እስር ላይ ከዋሉ በኋላ የሰላም ስምምነቱ ዳመና ያጠላበት ይመስላል።
ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ዎባ ኣሪ ወረዳ ለጊዜው “ ምንነቱ ያልታወቀ “ ባሉት ተባይ የአርሻ ማሳቸው መወረሩን አርሶ አደሮች ተናገሩ ፡፡ ተባዩ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው የሰብሎችን ፈሳሽ በመምጠጥና በማድረቅ መሆኑን የተናገሩት አርሶአደሮቹ ተባዩ ከሳምንት በፊት በአካባቢው ከታየ በኋላ ቀስ በቀስ ወደ መንጋነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል ፡፡
loading
Comments