DiscoverDW | Amharic - News
DW | Amharic - News
Claim Ownership

DW | Amharic - News

Author:

Subscribed: 53Played: 3,495
Share

Description

News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
4704 Episodes
Reverse
ዩናይትድ ስቴትስ እና ሩስያ የዩክሬኑን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ የሰላም እቅድ ነድፈዋል።እቅዱ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ በትላልቅ ጉዳዮች ላይ በሰጥቶ መቀበል እንዲስማሙ ጥሪ ያቀርባል። የአውሮጳ ዲፕሎማቶች ግን እቅዱ የአውሮፓ ኅብረትና ዩክሬንን ባልተሳተፉበት የትም አይደርስም ሲሉ ቅሬታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።
በምዕራቡ ዓለም ኔፈረቲቲ ዘመናዊነትን በሚያሳዬ የማኅበረሰብ ዝግጅቶች ላይ መቃ አንገትዋን፤ የጫነችዉ ዘዉድን ምልክት እያደረጉ ያቀርቧታል። ኔፈረቲቲ የበርሊን ምልክት መሆንዋን የሚናገሩት ኢትዮጵያዊ የታሪክ ምሁር አንድ ቀን ወደ አገርዋ ወደ ግብፅ መግባትዋ እንደማይቀር ተናግረዋል። በጀርመን የሚገኙ ምሁራንም ይሄ ተስፋ እንዳላቸዉ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ኬንያ እና ሶማሊያ ድርቅ ሊከሰት እንደሚችል የኢጋድ የአየር ትንበያ ማዕከል አስጠነቀቀ።እንደ ትንበያው ከጎርጎሪያኑ ጥር 2026 ድረስ ከመደበኛ በታች የሆነ የዝናብ መጠን የሚጠበቅ በመሆኑ፤ በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ፣ ምስራቃዊ ኬንያ እና ደቡባዊ ሶማሊያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን አደጋ ላይ የሚጥል የከፋ ድርቅ ሊያጋጥም ይችላል።
በኢትዮጵያ የፀጥታ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች መልስ ካላገኙ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ምርጫ ሊሆን አይችልም ሲሉ የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ተናገሩ ። ፕሮፌሰር መረራ ለዶቼ ቬለ በተለይ እንዳሉት በተለይ በኦሮሚያ ክልል ያለው የፀጥታ ሁኔታ አሳሳቢ በመሆኑ ከክልሉ መንግስት ጋር መነጋጋር የግድ አስፈላጊ ኾኖ ተገኝቷል።
እናት ፓርቲ«ከቅንጅት ተሳትፎ በማግለል የእናት ፓርቲን እንቅስቃሴ መገደብ አይቻልም»ሲል መግለጫ አወጣ። ፓርቲዉ ትናንት ይህን መግለጫ ያወጣዉ፤ ምርጫ ቦርድ የ5 ፓርቲዎች ስብስብ ሆኖ ከተመሰረተዉ ከ«ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» ቅንጅት ዉስጥ ሰርዞኛል ሲል ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ለማነጋገር ያደረግነዉ ጥረት ለዛሬ አልተሳካም።
ሰውሰራሽ አስተውሎት በዓለም ላይ በፍጥነት እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ነው።ቴክኖሎጂው ትምህርትን ግላዊነት በማላበስ፣ በቂ አገልግሎት ለሌላቸው ተማሪዎች ተደራሽነትን በማሻሻል በአፍሪካ በትምህርት ላይ በጎ ተጽእኖ እያሳደረ ነው።ያም ሆኖ ቴክኖሎጂውፈተናዎችም አሉት።ባለሙያዎች ፈተናዎቹን ለመሻገር ቴክኖሎጂው የሚገዛበት ፖሊሲዎች ማውጣትን ይመክራሉ።
የ5 ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» የተሰኘው ቅንጅት ከመጭው ምርጫ በፊት የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ሰላም እንዲያሰፍን ጠየቀ። ትብብሩ ያለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ የታሰሩ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች እንዲፈቱም ጠይቋል። መንግስት ለዚህ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥም ትብብሩ ቀነ ገደብ አስቀምጧል።
«ተግባራዊ ባይሆኑ ተወያይተን የምወስዳቸው ጠንካራ እርምጃዎች ይኖራሉ። ዝርዝር ሄኔታውን በቅርቡ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።»
የውጭ ምንዛሪ ግብይት በአቅርቦት እና ፍላጎት እንዲወሰን ከተደረገ ወዲህ ኢትዮጵያ ከሸቀጦች የወጪ ንግድ የምታገኘው ገቢ ዕድገት ቢያሳይም ብር እየተዳከመ ነው። የወርቅ ኤክስፖርት መሻሻል ብር እንዲረጋጋ ሊያደርግ እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ ተስፋ አድርጓል። ሦስት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይት የምንዛሪ ገበያው ብር ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ይፈትሻል።
የእናት ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ጌትነት ወርቁ፤ ነገር ግን መንግሥት በሐገሪቱ ሰላም ካስከበረ፤ ጦርነቶች ቆመው፣ የታሰሩት ተፈትተው፣ ያኮረፉት ኃይሎች ጋር የውይይትና የድርድር ሁኔታዎች ከተካሄዱ ምርጫው ሊካሄድ እንደሚችል ተስፋቸውን ይገልጻሉ።
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ሊጠናቀቅ የቀረዉ ሦስት ወራት ገደማ ነዉ። ኮሚሽኑ ከህዝብ ያሰባሰባቸዉን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ለመንግሥት ያቀርባል።በሌላ በኩል በያዝነዉ 2018 ዓመት ብሔራዊ ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል። ይሁንና መንግሥት ከህዝብ ለተሰበሰቡት አጀንዳዎች ከምርጫ መፊት መልስ ለመስጠት ጊዜና አቅም ይኖረዉ ይሆን?
ህወሐት በአለፈው እሁድ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስትን የፕሪቶርያ ውል በመጣስ በትግራይ ግጭት ለመፍጠር በአፋር እና በምዕራብ ትግራይ ታጣቂዎች እየመለመለ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
ብሪታንያ፣ ካናዳ እና አውስትራሊያ በዛሬው ዕለት ለፍልስጤም መንግስትነት በይፋ እውቅና ሰጡ። ርምጃውን የፍልስጤም መብት ደጋፊዎች መደበኛ እውቅና ለማግኘት የመጀመሪያው ጥረት ነው ሲሉ፤ በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ ዘንድ ውግዘት አስከትሏል።
በወንዶች የ29 አመቱ ስባስቲያን ሳዌ ያሸነፈ ሲሆን፤ ይህ ውጤት በለንደን ማራቶን ካሸነፈ ከአምስት ወራት በኋላ የተመዘገበ መሆኑ ነው።በሴቶችም ሌኛዋ የሀገሩ ልጅ ሮዝሜሪ ዋንጂሩ ፉክክሩን በአንደኛነት ጨርሳለች።ባለፈው አመት በተካሄደው የበርሊን ማራቶን በወንዶች ሚልኬሳ ​​መንገሻ፤ በሴቶች ትግስት ከተማ ለኢትዮጵያ ድርብ ድል አስገኝተው ነበር።
ኢትዮጵያ ስትካፈልበት ከሰነበተችው 20ኛው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ሳታገኝ የመጨረሻውን ቀን እየጠበቀች ነው። ዛሬ ኢትዮጵያዉያ ሜዳሊያ ልታገኝ ትችላለች ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የሴቶች የ5000 ሜትር ውድድር ያለ ሜዳሊያ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት አራት ጄኔራልነትን ጨምሮ ለ66 ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንኖች ማዕረጎች ሰጠ። ሉቴናንት ጄኔራል አለምሸት ደግፌ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ደስታ አብቼ፣ ሉቴናንት ጄኔራል ይመር መኮንን እና ሉቴናንት ጀኔራል ድሪባ መኮንን ሙሉ ጄኔራል ሆነዋል።
የማሊ፣ ኒጀር እና የቡርኪናፋሶ መንግሥታ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተገረሱ በኋላ ከሁለት ዓመታት በፊት የተመሰረተዉ የሳህል ግዛቶች ህብረት (AES) በያዘዉ ያልተሟሉ ግቦች እና የኢኮኖሚ ተስፋዎች ብሎም ሚዛናዊ ያልሆኑ ጥቅሞች በማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪናፋሶ ትችቶች ገጥሞታል። ህብረቱ ዛሬ እስከ ምን ድርሶ ይሆን?
ደቡብ ሱዳን አዲስ የእርስ በርስ ግጭት አፋፍ ላይ ያለች ይመስላል። ከጎርጎረሳዉያኑ 2018 ጀምሮ በሃገሪቱ የነበረዉን ከፍተኛ የእርስ በእርስ ጦርነት ያስቆመዉ የሰላም ስምምነት በተለይ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር በአገር ክህደት እና በሌሎች ወንጀሎች ከተከሰሱ እና እስር ላይ ከዋሉ በኋላ የሰላም ስምምነቱ ዳመና ያጠላበት ይመስላል።
ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ዎባ ኣሪ ወረዳ ለጊዜው “ ምንነቱ ያልታወቀ “ ባሉት ተባይ የአርሻ ማሳቸው መወረሩን አርሶ አደሮች ተናገሩ ፡፡ ተባዩ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው የሰብሎችን ፈሳሽ በመምጠጥና በማድረቅ መሆኑን የተናገሩት አርሶአደሮቹ ተባዩ ከሳምንት በፊት በአካባቢው ከታየ በኋላ ቀስ በቀስ ወደ መንጋነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል ፡፡
ለሦስት ዓመት ተኩል በትብብር ሲሠሩ የቆዩ አምስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ዛሬ መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ቅንጅት መሠረቱ። "ኢትዮጵያ የህልውና አደጋ ውስጥ ናት" የሚለው ድምዳሜ የቅንጅቱ መመሥረት ዐቢይ መነሻ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል።
loading
Comments