DiscoverDW | Amharic - News
DW | Amharic - News
Claim Ownership

DW | Amharic - News

Author:

Subscribed: 53Played: 3,489
Share

Description

News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
3481 Episodes
Reverse
ለመሆኑ በቅርብ ዓመታት የዘር ማጥፋት ወይም የጦር ወንጀል የተፈፀመዉ ናይጄሪያ ይሆን? ብቻ ዶናልድ ትራምፕ 8 ጦርነት አስቁሜያለሁ ይላሉ፣ትራምፕ እንደ ጠቅላይ አዛዥ የሚያዘምቱት ጦር ሶማሊያን፣ የመንን፣ ኢራንን፣ የቬኑዙዌላ ጠረፍን ይደበድባል አሁን ደጎሞ ናጄሪያ ላይ እየዛቱ ነዉ
ቢያንስ 5 ኢትዮጵያውያን በደቡብ አፍሪቃ ባለፈው ሳምንት በታጣቂዎች ተገድለዋል። በደቡብ አፍሪቃ የተባበሩት የኢትዮጵያውን ማኅበረሰብ ማኅበርና አንድ የማኅበረሰብ አንቂ በጆሀንስበርግ እና አካባቢው እንዲሁም በደርባን ኢትዮጵያውያኑን የገደሉት ወንጀለኞች መሆናቸውን ለዶቼቬለ ተናግረዋል፤ ሌሎች ግድያዎችም ደርሰው ሊሆን ይችላልም ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሒደት ወደ “የመጨረሻ ምዕራፍ” ቢቃረብም ኦነግ፣ ኦፌኮ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓ እና እናት ፓርቲዎች እየተሳተፉ አይደለም። የትግራይ ሕዝብ እስካሁን በሒደቱ ውክልና እንደሌለው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነሮች ገልጸዋል። ሒደቱ የገጠሙት ተግዳሮቶች “አብዛኞቹ ፖለቲካዊ” መሆናቸውን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ ተናግረዋል።
ዶቼ ቬለን ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ተቋማት ያገለገለው፣የአንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ ዜናነህ መኮንን አንደኛ ሙት ዓመት ልዩ መታሰቢያ መርሐግብር አዲስ አበባ ውስጥ ተካሄደ። ''ታላላቆቻችን እናክብር፣ ከቀደሙት ምን እንማር?''፣ በሚል መርህ በተካሄደው የዜናነህ መታሰቢያ መርሐ ግብር ላይ፣ የቀድሞ የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ ተገኝተዋል።
በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በቀጠለው የምስራቅ እና የመካከለኛው አፍሪቃ ከ17 ዓመት በታች የእግር ኳስ ሻምፒዮና ዋሊያዎቹ የመጀመሪያ የምድብ ጫወታቸውን በድል ጀምረዋል። ኢትዮጵያዊቷ ልቅና አምባው የስፔይን ሶሪአ ከተማ የስምንት ሺ ሜትር የሀገር አቋራጭ የሩጫ ውድድር አሸንፋለች።
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ፕሪቶሪያ-ደቡብ አፍሪቃ ላይ ግጭትን የማቆም ስምምነት ከተፈራረሙ ባለፈዉ ጥቅምት 23 ሶስኛ ዓመቱን አስቆጥሯል። ሶስቱ ዓመታቱ ብዙዎች እንደሚሉት ሁለቱ ኃይላት በስምምነታቸው መሰረት ግዴታቸውን ያልተወጡበት ወይም ሊወጡ ያልፈለጉበት ሰላምም ግጭት ያልነበረበት ሆኖ ነው ያለፈው።
ብሪታኒያ የስደተኞች ቁጥርን ለመቀነስ የጥገኝነት ፖሊሲ ማሻሻያ ማድረጓን አስታወቀች
የውጭ ምንዛሪ ግብይት በአቅርቦት እና ፍላጎት እንዲወሰን ከተደረገ ወዲህ ኢትዮጵያ ከሸቀጦች የወጪ ንግድ የምታገኘው ገቢ ዕድገት ቢያሳይም ብር እየተዳከመ ነው። የወርቅ ኤክስፖርት መሻሻል ብር እንዲረጋጋ ሊያደርግ እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ ተስፋ አድርጓል። ሦስት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ውይይት የምንዛሪ ገበያው ብር ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ይፈትሻል።
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሥራ ሊጠናቀቅ የቀረዉ ሦስት ወራት ገደማ ነዉ። ኮሚሽኑ ከህዝብ ያሰባሰባቸዉን ጥያቄዎችና አጀንዳዎች ለመንግሥት ያቀርባል።በሌላ በኩል በያዝነዉ 2018 ዓመት ብሔራዊ ምርጫ መካሄድ ይኖርበታል። ይሁንና መንግሥት ከህዝብ ለተሰበሰቡት አጀንዳዎች ከምርጫ መፊት መልስ ለመስጠት ጊዜና አቅም ይኖረዉ ይሆን?
ህወሐት በአለፈው እሁድ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስትን የፕሪቶርያ ውል በመጣስ በትግራይ ግጭት ለመፍጠር በአፋር እና በምዕራብ ትግራይ ታጣቂዎች እየመለመለ እና እያስታጠቀ ነው ሲል ከሷል።
የዋጃ ከተማ ነዋሪ ወጣትም በባህር ወደ ሳውዲ አረቢያ ቢያመራም ተመልሶ መጥቷል፡፡አሁንም ለመሄድ ያስባል። በማዕበል ምክንያት፣ በረሃና ውሃ ጥም የሞቱ ጓደኞቹን ያስታውሳል፡፡ ዋጃ ላይ በጣም አልቋል እኔም እራሴ ስደተኛ ነኝ፤ መከራ አለ፤ ተስፋ ቆርጠህ ነው የምትሄደው ከዚህ ስትወጣ ሞትን ትመርጣለህ፤ ጓደኛ ሲነጠልህ ታየዋለህ፤ በርሃብ ይላል።»
በስደት ህይወት ለራሱም ሆነ ለሌሎች የስራ እድልን ፈጥሮ ወደ ሌላ የስኬት ምዕራፍ ስለማደግ የሚያማትረው ሙርቴሳ ፈይሶ ዓላማው በዚህም ለማብቃት አለመሆኑን ያስረዳል፡፡
የዶናልድ ትራምፕን ዳግም ወደ ፕሬዝዳንትነት መመለስን ተከትሎ የወጡ የስደተኞችን ጉዳይ የተመለከቱ ት ዕዛዞችና ህጎች ተፈጻሚ እየሆኑ ነው። ነው። በተለይ በአሜሪካ ስር ዓት ውስጥ ያልተመዘገቡ ስደተኞችን የማፈስና ወደ ሃገራቸው የመመለስ ዘመቻው በርካታ ኢትዮጵያውያንን ለጭንቀት መዳረጉንና በፍርሃት እቤታቸው እንዲቀመጡ እንዳስገደዳቸው ታውቋል።
«ምንም ተጽእኖ አያሳድርም» ሲሉ በልበ ሙሉነት ሀሳባቸውን የጀመሩት መሸሻ ሶስና ደስታ «ኢትዮጵያን የሚያሳድራት፣ የሚመግባት እግዚአብሔር ነው፤ ራሷ አሜሪካ ለራሷ ትወቅ እኛ እግዚአብሔር አለን አይጥለንም» በማለት መተማመን በአሜሪካ ሳይሆን በእግዚአብሔር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
በክልሉ ያለዉ የፀጥታ ችግር በትምህርት ዘርፉ ላይ ያሳደረዉ ተፅኖ የጎላ እንደሆነ የሚናገሩት የሰሜን ወሎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፍትህ ታደሰ የመማር ማስተማሩ የተቋረጠባቸዉን አካባቢዎች ዳግም ወደ ትምህርት ለማስገባት እየተሰራ ነዉ ነገር ግን በዞኑ የማንነት ጥያቄ ያለባቸዉ አካባቢዎች አሁንም ከመማር ማስተማር ዉጭ ናቸዉ ይላሉ
በትግራይ ያለው ፓለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ፥ ኢኮኖሚያዊ አለመረጋጋትም እየተስተዋለ ይገኛል። ነዋሪዎች ግጭት በመስጋት ከባንኮች ገንዘብ ማውጣት፣ ሸቀጦች መሸመት በስፋት ይስተዋላል። ፓለቲካዊ አለመረጋጋቱ ዘርፈ ብዙ ችግር እያስከተለ መቆየቱ የሚገልፁት ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች፥ ሁኔታው እንዳይባባስም ስጋት አላቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአቅም ማሻሻያ / ሪሚዲያል / ተማሪዎች “ ትምህርታችንን በአቅራቢያ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እንዳንማር ተከለከልን “ አሉ ፡፡ በፀጥታ ሥጋት እና በርቀት ምክንያት ወደ ሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች ሄደው ለመማር መቸገራቸውን ተማሪዎቹ እና ወላጆች ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል ፡፡
አቶ እስክንድር ነጋ የሚመሩት የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት በዉጪ ሸምጋዮች አማካይነት ከመንግሥት ጋር ድርድር ጀምሯል የሚሉ ዘገቦች ሰሞኑን ተሰራጭተዉ ነበር።የግንባሩ መሪ እስክንድር ነጋ ዛሬ እንዳሉት ግን ድርጅታዉ ድርድር አልጀመረም
በአፍሪካ ተጽዕኖ ለማሳደር የሚደረጉ ዘመቻዎች በተለይም በሩሲያ በከፍተኛ መጠን ጨምረዋል። ዶይቼ ቬለ የዘመቻዎቹን ዘዴዎች፣ ዓላማዎች እና በቀጠናዎች መካከል ያላቸውን ልዩነት ሰንዷል።
ባለፉት አምስት አመታት አሜሪካ ለኢትዮጵያ 7.6 ቢሊዮን ዶላር ርዳታ ሰጥታለች። ባለፈው ዓመት ብቻ ግጭት፣ ድርቅ እና የምግብ ዋስትና እጦት ለገጠማቸው ኢትዮጵያውያን የሕይወት አድን ርዳታ ለማቅረብ አሜሪካ 676 ሚሊዮን ዶላር ወጪ አድርጋለች። ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ የምትሰጠው ርዳታ ለ90 ቀናት እንዲቆም ያሳለፉት ውሳኔ ካሁኑ ተጽዕኖ አሳድሯል።
loading
Comments